Wednesday 11 December 2013

ምኒልክ ማነው ?


ምኒልክ ማነው ? ”


(የአንድ ተቋም ሰልጣኞች ጥያቄ)

በአዲስ አበባ ፒያሳ አካባቢ የጋዜጠኝነት ስልጠና የሚሰጥ ተቋም አለ፡፡ አሰልጣኙ ስለ ቃለ መጠይቅ (ቃለ ምልልስ) እያስተማሩ የተለያዩ ምሳሌዎች እያቀረቡ ያስረዳሉ፡፡ በመካከል ‹‹ ለመሆኑ አፄ ምኒልክ የት ተወለዱ? ›› ብለው ጠየቁ ለተግባር ልምምድ መድረክ ላይ ለነበሩት ሰልጣኞች ቡድን ውስጥ መልስ የሚሰጥ አልተገኘም፤ ከ35 በላይ ለሆኑኑት በክፍሉ ውስጥ ለሚገኙት ጥያቄውን ደገሙት ወዲያው ‹‹ የቤት ስራ ይሁን›› ብለው ወጡ፡፡ ከ3 ቀናት በኃላ ገና እንደገቡ ሁለት ሰልጣኞች እጅ አወጡ ‹‹ ሳይቀድሙን…….. ›› ብለው ያሰቡ ይመስላል፡፡ ለአንዱ ዕድል ሰጡ ‹‹ ለመሆኑ ምኒልክ ማነው ? ›› ብሎ የቤት ስራ የነበረው ለመምህሩ የክፍል ስራ አድርጎ ጠየቀ ፡፡ መምህሩም እየተገረሙ ወደ አንደኛው እጅ አውጥቶ ወደነበረው    ‹‹አንተስ መልስ ነው ? ›› አሉት፡፡ ‹‹ አይደለም የእኔም ጥያቄ ይሄው ነበር ›› አለና አረፈው፡፡
#መጠየቅ ያደርጋል ሊቅ; ይባላል በጎ ነው፡፡ ግን ስለ አፄ ምኒልክ ጽሑፍ@ ነጋሪ@ ….. ጠፍቶ ይሆን? እውነት ግን የአሁን ዘመን ወገኖች አብዛኞቻችን ስለ ቀደምት የኢትዮጵያ ባለውለታዎች እናውቅ ይሆን? ታዲያ ለልጆቻችንስ ማን አስረዳቸው ?ለማንኛውም ከተረዳሁት ጥቂቱን ልመስክር ፡፡

Thursday 5 December 2013

leyu leyu ልዩ ልዩ


ኢትዮጵያ እና ሩሳሌም ግንኙነት
ሩሳሌም ነገረ እግዚአብሔር በብሉይ ሆነ በዘመነ ክርስትና በስፋት የተገለጠባት ቅድስት ሀገር መሆኗ ይታወቃል፡፡ ሀገራች ኢትዮጵያም ከኢየሩሳሌም ሆነ ከሌሎች ቀደምት ሀገራት ጋር ያላትን ግንኙነት በስፋት የሚነግረን የመጀመሪያው ማስረጃ መጽሐፍ ቅዱስ ነው፡፡ ኢትዮጵያ በአምልኮተ እግዚአብሔር የኖረች በርካታ ድንቅ ነገር የተመሰከረላት ስለመሆኗ እና የመሳሰለውን መጽሐፍ ቅዱስ ከ 41 ጊዜ በላይ በመጥቀስ ገልጾታል፡፡ መዝ 67*31
ከክርስትና በፊት በብሎይ ኪዳን እምነትና ስርዓተ አምልኮ ከኢየሩሳሌም ቀጥሎ ሕገ ኦሪትን በመቀበል ሁለተኛዋ ሀገረ እግዚአብሔር የሆነችው ኢትዮጵያ ከተጓዳኝ ቅድስት ሀገር ኢየሩሳሌም ጋር የነበራት ግንኙነት ምን ጊዜም ሲዘከር የሚኖር ታሪካዊ ነው፡፡ ግንኙነቱም ይደረግ የነበረው
+ የብሉይ ኪዳን እምነትና ሥርዓተ ትውፊት በመጋራት

+ በዓመት አንድ ጊዜ ቅድስት ሀገር ኢየሩሳሌም ላይ በመገኘት  የፋሲካን   በዓል በህብረት በማክበር
+ አንድ ዓይነት ሕግ መጽሐፋዊ ተጠቃሚ በመሆን እና በመሳሰሉት ነው፡፡
ይህም ግንኙነት የሀገር ርቀት ሊገታው በማይችለው ሂደት ላይ የቱን ያህል ጸንቶ የኖረና የሚኖር መሆኑን ከታሪክ ብቻ ሳይሆን በአሁኑም ዘመን ጎልቶ ከሚታየው የባሕል ግንኙነት ለክብረ በዓል በርካታ ምዕመናን መጓዝና የዴር ሱልጣን ሁኔታ ማረጋገጥ ይቻላል፡፡ ኢትዮጵያም የመጀመሪያዋ የውጭ ግንኙነት ያረገችው ከኢየሩሳሌመ ጋር መሆኑንም ያመለክተናል የንግስቲቱ ጉዞ ቀድሞም ሀገራቱ ግንኙነት እንደነበራቸው ማስረጃ ነው፡፡