“መፋታትን እጠላለሁ ”ሚል 2÷16
ጋብቻ
እግዚአብሔር የፈቀደው ክቡር ነው በይበልጥም በስርዓተ ቤተክርስቲያን በንስሐ እና በቅዱስ ቁርባን የሚፈፀም ጋብቻ ቅዱስ ጋብቻ ነው፡፡
ኤፌ 5÷32 ማቴ 19÷5 ሆኖም ግን ጋብቻ የበዛውን
ያህል ፍቺም እየበዛ መሆኑ ግልፅ ነው በርካቶችም ወደ ፍቺ የሚያመራ ትዳር ውስጥ እንደሚገኙ ይናገራል ስለሆነም በዚህ እትም በምክረ
ካህን ዓምድ የፍቺ ምክንያቶችና ፍቺ እንዳይገጥም መፍትሔዎችን በጥቂቱ እናስነብባለን፡፡
እግዚአብሔር
ፍቃዱ በጽናት እንድንኖር ነው እንጂ ፍቺን እንደሚጠላ “መፋታትን እጠላለሁ” የሚለው አምላካዊ ቃል ያስረዳናል፡፡ ከጋብቻ በፊት
የመጠናናት ዓላማ ክፉ፣ደግ ጠባያቸውን ለይተው ተቻችለው ለመኖር መሰረት የሚጥሉበት ነው፡፡ ሆኖም ግን አንዳንዶች በአግባቡ ሳይጠናኑ
ወይም ስለ ጋብቻ ኑሮ በቂ ግንዛቤ ሳይኖራቸው ወደ ትዳር ሲገቡ ከመኖር ይልቅ ፍቺ ሲገጥማቸው ይታያል በርግጥ በዝሙትና በሀይማኖት
ልዩነት ፍቺ ሊኖር እንደሚችል ይታወቃል ከተስተካከሉ ወይም ችግራቸውን ካስወገዱና ከተስማሙ ከፍቺው ይልቅ አብሮ መኖር የተመረጠ
ነው፡፡ ሉቃ 16÷18 ማቴ 19÷9
በዘመናችን
በርካቶችን ለፍቺ የዳረጉ ነገሮች ምን ይሆኑ?